fbpx
AMHARIC

የፌደራል ጠቅላይ አቃቢ ህግ የ114 ተከሳሾች ክስ እንዲቋረጥለት ለፍርድ ቤት በጽሁፍ አቀረበ

በሽብር ወንጀል ተከስሰው በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የሚገኙትን ሁለት የዋልድባ መነኮሳት ጨምሮ የ114 ተከሳሾች ክስ እንዲቋረጥለት ለፍርድ ቤት ውሳኔ ማስተላለፉን የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ አስታወቀ፡፡ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ የጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ማዕረጉ አሰፋ የሁለቱ መነኮሳት ክሱ መቋረጡን ለዶይቼ ቬለ አረጋግጠዋል። “ክሳቸው እንዲቋረጥ ውሳኔ መሰጠቱ እውነት ነው። በፍርድ ቤት በኩል ስለሆነ የሚለቀቁት፤ መለቀቅ አለመለቀቃቸውን ማረጋገጥ አልቻልንም፡፡

ዞሮ ዞሮ አቃቤ ህግ ክሱን ካነሳ ፍርድ ቤቱ የሚቀጥልበት ሁኔታ አይኖርም” ብለዋል፡፡ ክሳቸው ተቋርጦላቸዋል ከተባሉት ውስጥ ሁለቱ የዋልድባ መነኮሳት የሽብር ክስ የቀረበባቸው በጎንደር ተከስቶ ከነበረው ተቃውሞ ጋር በተያያዘ እንደነበር አይዘነጋም፡፡

መነኮሳቱ “ከግንቦት ሰባት ጋር ግኙነት አላችሁ፤ ጫካ ውስጥ የሚገኙ ታጣቂዎችን ትረዳላችሁ” በሚል የቀረበባቸውን ክስ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲከታተሉ ቆይተዋል፡፡ ከዓመት በላይ በእስር የቆዩት መነኮሳቱ ለፊታችን ሚያዝያ 18 የፍርድ ቤት ቀጠሮ ተሰጥቷቸው ነበር፡፡

Share your thoughts on this post
%d bloggers like this:
Visit Us On TwitterVisit Us On YoutubeVisit Us On Instagram