fbpx
AMHARIC

ፌስቡክና ኢንስታግራም የመተግበሪያ አጠቃቀም ሰዓት ላይ ገደብ ማስቀመጥ የሚያስችል አዲስ ገፅ ይፋ አደረጉ

ፌስቡክና ኢንስታግራም ሰዎች የመተግበሪያ አጠቃቀማቸው ላይ የሰዓት ገደብ ማስቀመጥ እንዲችሉ የሚረዳ አዲስ ገፅ ይፋ ማድረጋቸው ተገለፀ።

ይህ አዲሱ ገፅ ሰዎች ፌስቡክን እና ኢንስታግራምን በሚጠቀሙበት ወቅት ምን ያህል ሰዓት እንደተጠቀሙ የሚያሳይ መልዕክት እንደሚያደርሳቸው ታውቋል።

የፌስቡክ ኩባንያና በስሩ የሚገኘው ኢንስታግራም አዲስ ይፋ ያደረጉት ገፅ ሰዎች በመተግበሪያዎች ላይ ያሳለፉትን ሰዓት መቆጣጠር እንዲችሉ ያደርጋል።

እንዲሁም ሰዎች በቀን ውስጥ መጠቀም የሚፈልጉትን የሰዓት ገደብ እንዲያስቀምጡ የሚያስችል መሆኑ ተነግሯል።

አዲሱ የሰዓት መገደቢያ የፌስቡክ ገፅ ሰዎች ምን ያህል ሰዓት እንደተጠቀሙ የሚያሳውቃቸው መልዕክት እንዲደርሳቸው ያደርጋልም ተብሏል።

ምንጭ፦ ሲኤንኢቲ

Share your thoughts on this post
%d bloggers like this:
Visit Us On TwitterVisit Us On YoutubeVisit Us On Instagram