ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፒዮ ጋር በስልክ ተወያዩ
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፒዮ ጋር በስልክ ተወያዩ።
በዚህ ውይይታቸው ወቅትም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶክተር አብይ በጠቅላይ ሚኒስትርነት በመሾማቸው የመልካም ምኞት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ያወጣው መግለጫ እንደሚጠቁመው፥ ኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ማሻሻያዎችን እያደረገች ባለችበት በአሁኑ ወቅት ዩናይትድ ስቴትስ ለኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ ጠንካራ ድጋፉን እንደሚያደርግ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አረጋግጠውላቸዋል።
ኤፍ.ቢ.ሲ
Share your thoughts on this post