fbpx
AMHARIC

ጀርመን ሙንስተር፦በተሽከርካሪ ጥቃት እግረኞች ተገደሉ

በምዕራብ ጀርመን ሙንስተር ከተማ የእግረኛ መንገድ ላይ የወጣ ተሽከርካሪ ዛሬ ቢያንስ አራት ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች እንደቆሰሉ ፖሊስ አስታወቀ።

በምዕራብ ጀርመን ሙንስተር ከተማ የእግረኛ መንገድ ላይ የወጣ ተሽከርካሪ ዛሬ በርካቶችን እንደገደለ እና እንዳቆሰለ ፖሊስ አስታወቀ። ፖሊስ ቢያንስ 30 ሰዎች መቁሰላቸውን እና የጭነት መኪናው አሽከርካሪ ሕይወቱን ማጥፋቱን ገልጿል። የደረሰው ጥቃት የሽብር ጥቃት ይሁን አይሁን ፖሊስ በማጣራት ላይ ይገኛል።እንዲሁም ሌሎች ሁለት ተጠርጣሪዎችን በመፈለግ ላይ ነው። ከሁለት ሰዓት ገደማ በፊት ወደ እግረኞች መንገድ ዘልቆ የገባው ተሽከርካሪ ውስጥ ፈንጂ መገኘቱ ተዘግቧል። የተለያዩ የዜና ምንጮች በጥቃቱ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ቢያንስ አራት እንደሆኑ በመዘገብ ላይ ይገኛሉ።

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ልደት አበበ – DW

Share your thoughts on this post
%d bloggers like this:
Visit Us On TwitterVisit Us On YoutubeVisit Us On Instagram