የ10ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ፈተና እየተሰጠ ነው
የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች የ2010 ዓ.ም ሃገር አቀፍ ፈተና መውሰድ ጀመሩ።
የዘንድሮው የ10ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ፈተና ዛሬ መሰጠት ጀምሯል።
ፈተናው ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዓርብ ድረስ የሚሰጥ ይሆናል።
ፈተናውን ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ ተማሪዎች እንደሚወስዱ ሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች ኤጄንሲ አስታውቋል።
ፈተናው በመላ ሃገሪቱ በተቋቋሙ 2 ሺህ 709 የፈተና ጣቢያዎች እየተሰጠ ይገኛል።
የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ብሄራዊ ፈተና ደግሞ ከፊታችን ሰኞ ግንቦት 27 እስከ ግንቦት 30 ቀን 2010 ዓ.ም ይሰጣል።
ኤፍ.ቢ.ሲ
Share your thoughts on this post