fbpx
AMHARIC

የተለያዩ ሀገራት የግንቦት 20 ድል በዓል የመልካም ምኞት መልዕክታቸውን እየላኩ ነው

ዛሬ እየተከበረ ያለውን የግንቦት 20 ድል በዓልን ምክንያት በማድረግ የተለያዩ ሀገራት መሪዎች የመልካም ምኞት መልዕክታቸውን ለኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት እየላኩ ይገኛሉ ።

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፒዮ በፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና አሜሪካ ህዝብ ስም የግንቦት 20 ድል የመልካም ምኞት መልዕክታቸውን ልከዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው ኢትዮጵያ እና አሜሪካ የጠለቀ እና የረዥም ጊዜ ወዳጅነት እንዳላቸው አንስተዋል።

ይህ ወዳጅነታቸው ዘላቂ ልማት፣ ዴሞክራሲ፣ የሰብዓዊ መብት፣ ሰላም እና መልካም አስተዳደር ማምጣት ላይ የተመሰረተ መሆኑንም ነው የገለፁት።

ለኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ መልካም ምኞታቸውን ያስተላለፉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፥ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት እና በቅርብ ዓመታት ሀገሪቱ የተጎናፀፈችውን የምጣኔ ሀብት እድገት ለማስቀጠል ላላቸው ቁርጠኝነት የአሜሪካ ሙሉ ድጋፍ እንዳላቸውም ነው ያረጋገጡት።

የሁለቱ ሀገራት ወዳጅነት የበለጠ እንዲያድግም የዩናይትድ ስቴትስ ዝግጁነትንም ደግመው አረጋግጠዋል።

በተጨማሪም የሳዑዲ አረቢያው ንጉስ ሳልማን እና ልዑል አልጋ ወራሽ መሀመድ ቢን ሳልማን ለኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሙላቱ ተሾመ በላኩት መልዕክት ነው መልካም ምኞታቸውን ያስተላለፉት።

የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ፕሬዚዳንት ሼክ ከሊፋ ቢን ዛይድ አል ነኸን የመልካም ምኞት መልዕክታቸውን ልከዋል።

እንደዚሁ የሰሜን ኮሪያ ብሄራዊ ሸንጎ ፕሬዚዳንት ኪም ዮንግ ናም በተመሳሳይ የግንቦት 20 ድል በዓል መልካም ምኞታቸውን ልከዋል።

ኤፍ.ቢ.ሲ

Share your thoughts on this post
%d bloggers like this:
Visit Us On TwitterVisit Us On YoutubeVisit Us On Instagram