የሩዋንዳው ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ በሃዋሳ ይፋዊ የእራት ግብዣ
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በኢትዮጵያ ጉብኘት በማድረግ ላይ ለሚገኙት የሩዋንዳው ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ በሃዋሳ ይፋዊ የእራት ግብዣ አሰናድተውላቸዋል።
በእራት ዝግጅቱ ላይ የሩዋንዳው ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ ከኢትዮጵያ አጠቃላይ የልማት እንቅስቃሴ እና ጥረት አገራቸው የምትማረው ብዙ ነገር እንዳለ ገልፀዋል።
ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ ጋር በሁለትዮሽና የአፍሪካ ጉዳዮች ላይ ተባብረው ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ጠቅሰው ዶ/ር አብይ ሩዋንዳን እንዲጎበኙ ጋብዘዋል።
የሩዋንዳው ፕሬዚዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ላደረጉላቸው ግብⶳ አመስግነዋል።
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ ፕሬዚዳንት ካጋሜ ሩዋንዳን ከእርስ በእርስ ጦርነት ወደልማት የመሩ ፖለቲከኛ ናቸው ብለዋል፤ በአፍሪካ የሰላምና ደህንነት ጉዳይ ላይ ካጋሜ ገንቢ አስተዋጽኦ ያደረጉ መሆናቸውን በመግለፅም የአፍሪካ መስራች አባቶችን የሰላምና የልማት ራዕይ ለማሳካት በጋራ እንሰራለን ብለዋል።
በሀዋሳ በነበራቸው ጉብኝት በክልሉ እይተሰሩ ባሉ የኢንዱስትሪ ፓርክ ልማት መደሰታቸውን ገልጸው የክልሉ ህዝብ ላደረገላቸው ደማቅ አቀባበል የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል።
በሁለቱ ሀገራት ያለው የወንድማማች ግንኙነት የበለጠ እንዲጠናከር እጅ ለእጅ ተያይዘው መጓዝ እንዳለባቸው ጠቅሰው፤ በክልሉ እና በጠቅላይ ሚኒስትሩ ለተበረከተላቸው ስጦታ አመስግነዋል።
Source:- MOFA