fbpx
AMHARIC

አንድ ጊዜ ተዘርተው ለ10 እና 20 አመታት በውሀ ብቻ ምርት የሚሰጡ የጤፍ እና ማሽላ ዝርያዎች በምርምር ተገኙ

የሳይንስ እና ቴክኖሎጅ ሚኒስቴር አንድ ጊዜ ተዘርተው ለ10 እና 20 አመታት በውሀ ብቻ ምርት መስጠት የሚችሉ የጤፍ እና ማሽላ ዝርያዎች በምርምር መገኘታቸውን አስታወቀ።

የተገኘው የጤፍ ዝርያ አንድ ጊዜ ከተዘራ በኋላ ለ10 አመት የማይሞት እና በየሶስት ወሩ ውሀ ብቻ ካገኘ ምርት መስጠት የሚችል ነው ተብሏል።

የማሽላው ዘርያ ደግሞ አንድ ጊዜ ተዘርቶ ለ20 አመት ድጋሚ መዝራት ሳያስፈልግ በየሶስት ወሩ ምርት መስጠት ይችላል ነው የተባለው።

አሁን ላይም ዝርያዎቹን ለሃገሪቱ ገበሬዎች ለማከፋፈል የዘር ብዜት ስራ እየተሰራ ሲሆን፥ ዝርያዎቹ በ2011 የምርት ዘመን ለገበሬው የሚከፋፈሉ ይሆናል።
በኢትዮጵያዊ ተመራማሪ የተገኙት እነዚህ ዝርያዎች የኢትዮጵያን የሰብል ልማት ታሪክ መቀየር እንደሚችሉ ታምኖባቸዋል።

በቤተልሄም ጥጋቡ – ኤፍ ቢ ሲ

Share your thoughts on this post
%d bloggers like this:
Visit Us On TwitterVisit Us On YoutubeVisit Us On Instagram