fbpx
AMHARIC

አማዞን የሰዎችን ማንነት በፊት ብቻ መለየት የሚያስችለውን መሳሪያ ለገበያ እንዳያቀርብ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች አሳሰቡ

የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች የሰዎችን ማንነት በፊት ብቻ መለየት የሚያስችለው መሳሪያ አማዞን ለመንግስት እና ሌሎች መሳሪያን ለሚፈልጉ አካላት ማቅረብ እንደሌለበት አሳሰቡ።

ተሟጋቾቹ ይህ መሳሪያ በስደተኞች እና በቆዳ ቀለም ምክንያት ሰዎች ተፅዕኖ እንደሚደርስባቸው የሚያደርግ በመሆኑ ተግባራዊ መሆን የለበትም ብለዋል።

ከ40 በላይ የሚሆኑት የመብት ተሟጋቾች ለአማዞን የኦንላይን ገበያ ስፍራ ባለቤት ለሆኑት ጆፍ ቤዞስ በላኩት ደብዳቤ ይህ መሳሪያ ሰዎች አላግባብ ጥቃት እንዲደርስባቸው እና መንግስት ተገቢ ያልሆነ ክትትል ስርዓት እንዲዘረጋ ያደደርጋል ብለዋል።

አማዞን በበኩሉ መሳሪያው ወንጀል የፈፀሙ ለማወቅ፣ ዝነኞችን ለመለየት እና የህብረተሰቡን ደህነት ለመጠበቅ እንደሚውል ነው በፈረንጆቹ 2016 ይፋ አድርጓል።

ከበርካታ ሚሊየን ሰዎች ስብስብ መካከል መሳሪያው የተለያ ፍላጎት ያላቸውን ሰዎቸ በቅፅበት በመለየት ወንጀል ለመከላከል እንደሚያስችል ነው አማዞን ያስታወቀው።

የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾቹ ለጆፍ ቦዘስ በላኩት ደብዳቤ ይህ ሁኔታ ሰዎች በጎዳኖች የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ ነፃነት የሚገድብ እንደሆነ ገልፀዋል።

መሳሪያውን የሚጠቀሙ ሰዎች የህግ ድጋፍ ያላቸው እና በአግባቡ ለመጠቀም ሀላፊነት ሊወስዱ የሚችሉ መሆናቸው ተረጋግጦ የሚሰጥ ነው ተብሏል።

ከአማዞን በተጨማሪ ጎግል እና ማይክሮሶፍት ይህን መሳሪያ እንደሚያቀርቡ ተነግሯል።

ምንጭ:- ሮውይተርስ

Share your thoughts on this post
%d bloggers like this:
Visit Us On TwitterVisit Us On YoutubeVisit Us On Instagram