fbpx
AMHARIC

በህገ ወጥ መንገድ በመተማ በኩል ሀገር ውስጥ ሲገቡ የነበሩ 58 ክላሽ እንኮቮች ተያዙ

በመተማ በኩል ህገ ወጥ መሳሪያዎች በተለያዩ ቀናት ወደ ሀገር ውስጥ ሊገቡ ሲሉ በቁጥጥር ስር ዋሉ።

በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ ሲገቡ የተያዙት የጦር መሳሪያዎች 58 ክላሽ እንኮቮች እና 4 ሺህ 354 ጥይቶች እንደሆኑ የምዕራብ ጎንደር ዞን የመተማ ወረዳ ፓሊስ ፅህፈት አስታውቋል።

ግንቦት 12 ቀን 2010 ዓ.ም ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት በመተማ ወረዳ ደለሎ ቀበሌ 33 ክላሽ እንኮቭ ጠብመንጃ 3 ሺህ 970 ጥይቶች በቁጥጥር ስር ማዋል ተችሏል።

እንዲሁም ግንቦት 13 ቀን 2010 ዓ.ም በመተማ ዮሐንስ ከተማ በመንገድ ላይ በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ 25 ሽጉጦች ከ384 ጥይቶች በፀጥታ አካላትና በመከላከያ ሠራዊት አባላት ቅንጅታዊ ክትትል ለመያዝ መቻሉን የጽህፈት ቤቱ ኃላፊና የኮማንድ ፖስት አባል ኢንስፔክተር አብራራው የኋላ ተናግረዋል ።

መሳሪያዎቹና ጥይቶቹን በትራክተር ጭኖ ለማስገባት የሞከሩ ሁለት አዘዋዋሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው እየተጣራ መሆኑም ነው የተመለከተው።

ሌሎች በዚህ ወንጀል የተሳተፉ አካላትን ለመያዝ ከፍተኛ ክትትል እየተደረገ እንደሆነ ታውቋል።፡፡

የድንበር አካባቢ በመሆኑ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር በከፍተኛ ሁኔታ እንዳለ የተገለፀ ሲሆን፥ ችግሩን ለመቅረፍ ህብረተሰቡን በመሳተፍ ጥብቅ የቁጥጥር እና የክትትል ሥራ እየተከናወነ መሆኑ ተነግሯል።

 

ምንጭ፦ ኢዜአ

Share your thoughts on this post
%d bloggers like this:
Visit Us On TwitterVisit Us On YoutubeVisit Us On Instagram