ሰበር ዜና – ፕሪምየር ሊጉ ይቋረጣል
ሰበር ዜና- ፕሪምየር ሊጉ ይቋረጣል
በኢትዮጵያ እግርኳስ እየተፈጠሩ በሚገኙ ጉዳዮች ዙርያ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን 16 የፕሪምየር ሊግ ክለቦችን ስብሰባ ጠርቷል፡፡ ስብሰባቸው ሀሙስ ሚያዝያ 25 ቀን 2010 በጁፒተር ሆቴል የሚከናወን ሲሆን የ23ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በዚህ ሳምንት እንደማይካሄዱ እና የሊጉ እጣ ፈንታ በምክክር ጉባዔ እንደሚወሰንም የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ጁነይዲ ባሻ ለሶከር ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል፡፡
ምንጭ፡- ሶከር ኢትዮጵያ
Share your thoughts on this post