fbpx
AMHARIC

ጨፌ ኦሮሚያ ሊያካሂድ የነበረውን 7ኛ መደበኛ ጉባዔ ለሌላ ጊዜ አዛወረ

ጨፌ ኦሮሚያ ሊያካሂድ የነበረውን 7ኛ መደበኛ ጉባዔ ወደ ሌላ ጊዜ ማዛወሩን የጨፌ ኦሮሚያ ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

የጨፌ ኦሮሚያ 7ኛ መደበኛ ጉባኤ ከየካቲት 30 እስከ መጋቢት 1 ቀን 2010 ዓ.ም እንደሚካሄድ መነገሩ ይታወሳል።

የጨፌ ኦሮሚያ ጽህፈት ቤት የኮሙዩኒኬሽን እና የመረጃ አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ደምሴ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደተናገሩት፥ በአካባቢው ያለው የሰላም ሁኔታ የተረጋጋ ባለመሆኑ የጨፌው መደበኛ ስብሰባ ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝሟል።

የጨፌ ኦሮሚያ 7ኛ መደበኛ ጉባኤ የሚካሄድበትን ቀን አስመልክቶ ወደ ፊት ለጨፌው አባላት በሚደረግ ጥሪ የሚታወቅ መሆኑንም አቶ ሀብታሙ አስታውቀዋል።

Share your thoughts on this post
%d bloggers like this:
Visit Us On TwitterVisit Us On YoutubeVisit Us On Instagram