fbpx
AMHARIC

የአውሮፓ ህብረት ከቀድሞው የሩሲያ ሰላይ መመረዝ ጋር በተያያዘ አምባሳደሩን ከሞስኮው ሊያስወጣ ነው

በሀገረ ብሪታኒያ ሩሲያ በቀድሞው የስለላ አባሏ ላይ በነርቭ ኬሚካል መርዛለች በማለት የአውሮፓ ህብረት መሪዎች ምክር ቤት በሩሲያ ያለውን አምባሳደሩ ከመጥራት ውጭ ሌላ ምንም አማራጭ እንደሌለ በመስማማቱ ነው፡፡

የብሪታኒያ ጠቅላይ ሚንስትር ቴሬሳ ሜይ በሀገራቸው ሩሲያ የፈፀመችው የነርቨ ጥቃት አውሮፓ ህብረትን ከመውረር የማይተናነስ ድርጊት ነው ሲሉ ገልፀውታል፡፡

ይሁን እንጂ ሩሲያ ድርጊቱን አለመፈፀሟን በመግለጽ ለነርቩ ጥቃቱ ሀላፊነት እንደማትወስድ አስታውቃለች፡፡

ባለፈው የካቲት 25 የነርቨ ኬሚካል ጥቃት የተፈፀመባቸው ሰርጌይ ስክሪፓል እና ልጁ ጁሊያ በአሁን ወቅት በአሳሳቢ የጤና ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙ ተነግሯል፡፡

የጋራ የደህንነት ስጋት በሆነው በዚህ ፈታኝ ወቅት ህብረቱ ከብሪታኒያ ጎን እንደሚሰለፍ የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ገልጿል፡፡

የብሪታኒያ ጠቅላይ ሚንስትር ሜይ የነርቭ ጥቃቱን ሩሲያ መፈፀሟን የሚያሳይ ማስረጃ ሲያቀርቡ ኬሚካሉን ሩሲያ በባለፉት 10 ዓመታት ውስጥ እንዳመረተችው ተናግረዋል፡፡

ምንጭ፦ ቢቢሲ

 

Share your thoughts on this post
%d bloggers like this:
Visit Us On TwitterVisit Us On YoutubeVisit Us On Instagram