fbpx

HT

ሐበሻ ታይምስ ሚዲያ

AMHARIC

አፕል ወላጆች የህጻናት ልጆችን የስልክ አጠቃቀም መቆጣጠር የሚያስችል ገጽ ይፋ አድርጓል

አፕል ወላጆች የልጆቻቸውን የስማርት ስልኮችን አጠቃቀም መቆጣጠር እና መገደብ የሚያስችል ገጽ ለወላጆች አቅርቧል፡፡
በባለፈው ጥር ወር ሁለት ታዋቂ ባለሃብተች የአፕል የስማርት ስልኮችን ለህጻናቶች የተመቸ አጠቃቀም እንዲኖር የማድረግ ስራዎችን አልሰራም በሚል መንቀፋቸውን እና ተቋሙ ወላጆች የልጆቻቸውን አጠቃቀም መከታተል የሚያስችሉ አማራጮችን እንዲያቀርብ ጥሪ አቅርበው ነበር፡፡ ህጻናት ለአይፎን ያላቸው ፍቅር ከፍ ያለ መሆኑ ደግሞ በአፕል ተቋም ላይ ችግሮችን እየፈጠረ መሆኑ ይነገራል፡፡
አፕልም ይህን ወቀሳ ተከትሎ ወላጆች ህጻናት ልጆቻቸው መች እና እንዴት የአይፎን የስማርት ስልኮች እንደተጠቀሙ የሚያሳይ ምቹ ሁኔታን የመፈጠረ ገጽ አቅርቧል፡፡
አዲሱ የወላጆች ገጽም apple.com/families — በሚለው ወላጆች ገብተው ማግኘት እንደሚችሉ የገለጸው ተቋሙ በገጹ አማካኝነት ወላጆች የህጻናት ልጆቻቸውን አድራሻ፣ አጠቃቀማቸውን የመቆጣጠር እና መወሰን እንዲሁም ህጻናቱ በስልኮቻቸው የሚጠቀሙዋቸውን ይዘቶች የማጥለል ተግባራትን መከወን ያስችላል ተብሏል፡፡
የኮመን ሴንስ ተቋም ያወጣው የጥናት ውጤት 98 ከመቶ ህጻናቱ በቤት ውስጥ የሚጠቀሙዋቸው የሞባይል ስልኮችን ሲሆኑ በቀን በአማካኝ 48 ደቂቃዎችን በስልኮቻቸው አንደሚያሳልፉ ጠቅሷል፡፡ ከእነዚህ ታዳጊዎች መካከልም 42 በመቶዎቹ የራሳቸው ስልክ ያላቸው እንደሆነ ጥናቱ አመልክቷል፡፡


ምንጭ:- ሲኤንኤን

Share your thoughts on this post
%d bloggers like this:
Visit Us On TwitterVisit Us On YoutubeVisit Us On Instagram