
በ1990 የድንበር ጦርነቱ ሲቀሰቀስ አዲስ አበባ ውስጥ ለሁለት አስርታት ተዘግቶ ከቆየው የኤርትራ ኤምባሲ በሮች በኤርትራ ባለስልጣናት ሲከፈት ክፍሎች ውስጥ በአቧራ የተሸፈኑ መኪኖች፣ የቤት ውስጥ እቃዎች እና የተለያዩ መጠጦች ባሉበት ተገኝተዋል።
ጦርነቱ በ1992 ቢያበቃም ግንኙነታቸው ሻክሮ እስካሁን ድረስ ቆይቶ ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ወደ ኤርትራ መጓዛቸውን ተከትሎ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ ነው ኤምባሲው መልሶ የተከፈተው።
እነዚህ ፎቶግራፎች የኤርትራ ኤምባሲ ዛሬ ሲከፈት በቢቢሲ የተነሱ ናቸው።






የፎቶግራፎቹ ባለቤትነት መብት በሕግ የተጠበቀ ነው
BBC Amharic
Share your thoughts on this post