fbpx
AMHARIC

በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ወደ ቀጣዩ ዙር ያለፈው ወላይታ ድቻ አዲስ አበባ ገባ

በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ የግብፁን ዛማሌክ ክለብ በመርታት ወደ ቀጣዩ ዙር ያለፈፉት የወላይታ ድቻ እግር ኳስ ክለብ ቡድን አባላት አዲስ አበባ ገቡ።

የወላይታ ድቻ የእግር ኳስ ክለብ አባላት አዲስ አበባ ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም የክለቡ ደጋፊዎች እና የስፖርቱ ቤተሰቦች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ባሳለፍነው እሁድ በካይሮ አል-ሰላም ስታዲየም በተካሄደ የመልስ ጨዋታ 90 ደቂቃውን በዛማሌክ 2 ለ 1 መሪነት በመጠናቀቁ ድምር ውጤቱ 3 አቻ በማለቁ የመለያ ምት ተሰጥቶ ወላይታ ድቻ በመለያ ምት ዛማሌክን ማሸነፉ ይታወሳል።

ወላይታ ድቻ በኮንፌዴሬሽን ዋንጫ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታ በሃዋሳ አለም ቀአፍ ስታዲየም የግብፁን ዛማሌክን በማስተናገድ 2ለ1 ማሸነፉም ይታወሳል።

ወላይታ ድቻ በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ቅድመ ማጣሪያም የዛንዚባሩን ዚማሞቶ ክለብን በደርሶ መልስ ውጤት 2ለ1 በመርታት ነበር ከግብፁ ዛማሌክ ጋር የተገናኘው።

የወላይታ ድቻ እግር ኳስ ክለብ የዛንዚባሩን ክለብ ዚማሞቶ ቅድመ ማጣርያ በመርታት ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፍን ተከትሎ ለእያንዳንዱ ተጫዋች የ20 ሺህ ብር የማበረታቻ የገንዘብ ድጋፍ አድርጎ ነበር።

ክለቡ በመጀመሪያው ዙር ጨዋታም የግብፁ ዛማሊክን ማሸነፉን ተከትሎ የቡድኑ ተጫዋቾች እያንዳንዳቸው 20 ሺህ ብር ሽልማት እንዳበረከተላቸው ይታወሳል።

ወደ ግብፅ በማቅናት ዛማሌከን በማሸነፍ ዛሬ ወደ አዲስ አበባ የገቡት የወላይታ ድቻ ተጫዋቾች የተለያዩ የማበረታቻ ሽልማቶች እንደሚበረከቱላቸው የሚጠበቅ ሲሆን፥ ሶዶ እና ሀዋሳ ላይም ደማቅ አቀባበል ይደረግላቸዋል ተብሏል።

ኤፍ.ቢ.ሲ

Share your thoughts on this post
%d bloggers like this:
Visit Us On TwitterVisit Us On YoutubeVisit Us On Instagram