fbpx

HT

ሐበሻ ታይምስ ሚዲያ

AMHARICPOLITICSWORLD

ሰሜን ኮሪያ የኒውክለር ጦር መሳሪያ ሙከራዋን ለማቆም ተስማማች

ሰሜን ኮርያ ከአሜሪካ ጋር ውይይት የምታደርግ ከሆነ የኒውክሌርና ሚሳኤል ሙከራዋን እንደምታቋርጥ ገለጸች፡፡

ሀገሪቱ እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰችው ከደቡብ ኮሪያ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር በፒዮንግያንግ ባደረጉት ውይይት ነው ተብሏል፡፡

ሆኖም ሰሜን ኮሪያ የኒውክለር ጦር መሳሪያ ሙከራዋን የምታቆመው የሀገሯ ደህንነት ዋስትና ሲያገኝ መሆኑን በሰሜን ኮሪያ ጉብኝት እያደረጉ የሚገኙ የደቡብ ኮሪያ ከፍተኛ የፀጥታ አማካሪ ተናግረዋል፡፡

የሰሜን ኮሪያ መሪ ኪም ጆንግ ኡንና የደቡብ ኮሪያ አቻቸው ሙን ጄ ኢን ‹‹ፓንሙንጁም›› በተባለ የሰሜን ኮሪያ ግዛት በፊታችን ሚያዚያ ወር ተገናኝተው እንደሚወያዩም አልጄዚራ ዘግቧል።

Share your thoughts on this post
%d bloggers like this:
Visit Us On TwitterVisit Us On YoutubeVisit Us On Instagram