fbpx
AMHARIC

ሩሲያ 23 የብሪታኒያ ዲፕሎማቶችን በዚህ ሳምንት ከሀገሯ እንድምታስወጣ አስታወቀች

ብሪታንያ በሀገሯ የሚገኙ 23 የሩሲያ ዲፕሎማቶችን በአንድ ሳምንት ለቀው እንዲወጡ ማሳወቋን ተከትሎ ሩሲያም በሀገሯ የሚገኙ 23 የብሪታንያ ዲፕሎማቶችን እንደምታስወጣ የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።

በሞስኮ ከሚገኘው የብሪታንያ ኤምባሲ ዲፕሎማቶችን በዚህ ሳምንት እንደምታስወጣ ነው ይፋ ያደረገችው።

ከዚህ በተጨማሪም በሞስኮ የሚገኘውን የብሪትሽ ካውንስልን እና በቅዱስ ፒተርስበርግ የሚገኘውን የእንግሊዝ ቆንስላ ፅህፈት ቤትን ልትዘጋ እንደምትችልም ገልጻለች።

በዚህ ሳምንት በሳልስ በሪይ በአንድ የቀድሞ የሩሲያ ሰላይ የነርቭ ጥቃት የተፈፀመበት ሩሲያ ሰራሽ መርዝ እንዴት ጥቅም ላይ እንደዋለ ማብራሪያ ሞስኮ እንድትሰጥ የጊዜ ገደብ ያስቀመጠችው ብሪታኒያ 23 በሀገሯ የሚገኙ የሩሲያ ዲፕሎማቶች በአንድ ሳምንት ውስጥ እንዲወጡ ማዘዟ የሚታወስ ነው።

ሩሲያ በብሪታንያ በኩል የቀረባባትን ክስ ውድቅ ማድረጓም የሚታወቅ ነው።

የምንጭ፦ ቢቢሲ

Share your thoughts on this post
%d bloggers like this:
Visit Us On TwitterVisit Us On YoutubeVisit Us On Instagram